Heading

HOMEAbout UsMunicipal OrgansProjectsNEWSContact UsFeedback

መመመመመመመመመመመመ

Municipal News

መመመመመመመመመመመ

 

Harar Municipality Lend Br.1million to Sheikh Abubakar School

Posted on Wednesday, May 07, 2008

It is noticed that Sheikh Abubakar School has started constructing a three storey market building in order to generate an income to the school. The construction work (the project) has been undertaken by a long term loan fund from the World Islamic Development Bank. According to the Waqf committee head, Abdullahi Wabar, the construction of the project has stopped since last year mainly due to lack of fund. In this regard the Harar municipality has given a due attention to the project and lend one million birr to the school in order to accomplish the project.

በሐረር ከተማ የመሬት የሊዝ እዳ አከፋፈል ውዝግብ አስነሳ

Posted on Thursday, May 01, 2008

በሐረር ከተማ የተሰማሩ ኢንቨስተሮች ከአስር አመት በላይ የተጠራቀመ የመሬት የሊዝ እዳ ክፍያ እንድንከፈል ተጠይቀናል ሲሉ አማረሩ፡፡ የከተማው መስተዳድር የክፍያው ሁኔታ ፍትሐዊ መሆኑን በመግለፅ አቤቱታውን አስተባበለ፡፡

 

በሐረር ከተማ በኢንቨስትመንት መስክ የተሰማሩ ባለሀብቶች፤ ከ1986 ዓ.ም. ጀምሮ ታሳቢ የሚደረግ የሊዝ እዳ ክፍያ መጠየቃቸውን በመግለፅ፤ የእዳ እሳቤውን ተቃወሙ፡፡ ባለሀብቶቹ አንደኛ ደረጃ በካሬ ሜትር 650 ብር ሁለተኛ ደረጃ 550 ብር፣ ሦስተኛ ደረጃ 5ዐዐ ብር ታሳቢ የሚደረግ ክፍያ መጠየቃቸውን አስታውቀዋል፡፡ በዚህም የመሬት ርክክብ ሲደረግ የክፍያ መጠኑ ያልተወሰነ መሆኑን በመጥቀስ ፍትሐዊ ያልሆነ ከፍተኛ ክፍያ መጠየቃቸውን ገልፀዋል፡፡


ባለሀብቶቹ ከከተማው አስተዳደር ጋር የኢንቨስትመንት ውል ሲገቡ የክፍያ መጠን ካሬ ሜትር ተተምኖ ያልተገለፀላቸው መሆኑን በመጥቀስ፤ አስተዳደሩ ያስታወቃቸው የሊዝ ክፍያ መጠን ድንገተኛ እንደሆነባቸው ገልፀዋል፡፡ በዚህም "የከተማው አስተዳደር ከውል ውጪ ከፍተኛ ክፍያ ጠይቆናል" ሲሉ አማርረዋል፡፡

ባለሀብቶቹ የከተማው አስተዳደር የክፍያ ሁኔታውን ለረዥም ጊዜ ሳያሳውቃቸው ቆይቶ፤ በያዝነው ወር ድንገተኛ የክፍያ ውዝፍ መግለፁን ተቃውመዋል፡፡ በተሰጣቸው መሬት ላይ ግንባታ ማከናወናቸውን በመጥቀስ፤ በቅርቡ የተገለፀላቸውን የሊዝ እዳ ለማስከፈል አስተዳደሩ በመሬቱ ላይ የገነቡትን ግንባታ በመያዣነት እንደያዘባቸው ገልፀዋል፡፡

በተጨማሪም የከተማው አስተዳደር ከአስር ዓመት በላይ የተጠራቀመውን እዳ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲከፍሉ ማስገደዱን ጠቅሰዋል፡፡ እንደ ባለሀብቶቹ ገለፅ አንድ ባለሀብት በሊዙ እሳቤው ከአንድ እስከ አራት ሚሊዮን ብር ለመክፈል የሚገደድ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ባለሀብቶቹ የሊዝ ክፍያውን በመቃወም የፊርማ ማሰባሰብ ሥራ መጀመራቸውን ገልፀዋል፡፡ የተቃውሞ ፊርማውንም ለሚመለከታቸው የከተማው፣ የክልሉና የፌደራል መንግሥት አመራሮች እንደሚያስታውቁ ገልፀዋል፡፡

የሐረር ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ አሪፍ መሀመድ በበኩላቸው የክልሉ ምክር ቤት እስከ 1999 ዓ.ም. ድረስ የሊዝ ደንብ ያልነበረው መሆኑን ጠቅሰው፤ "የሊዝ ደንቡ ትግበራ መዘግየቱ የክልሉ አስተዳደር ችግር ነበር" ሲሉ ገልፀዋል፡፡ አቶ አሪፍ የሊዝ ደንቡ ዘግይቶ ቢፀድቅም ኢንቨስተሮች እዳቸውን መክፈል እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡

የክፍያው ሁኔታ በተለያየ የከተማው የይዞታ ደረጃ በካሬ ሜትር ከ150 እስከ 650 ብር መሆኑን የገለፁት አቶ አሪፍ፣ ባለሀብቶች የሊዝ አዋጅ በፌዴራል ደረጃ ከወጣበት ከ1986 ዓ.ም. ጀምሮ ያለባቸውን እዳ መክፈል እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡ የአከፋፈሉ ሁኔታ ግን በአንድ ጊዜ አለመሆኑን ሥራ አስኪያጁ ገልፀው፤ የክፍያ ጊዜውን በተመለከተ መመሪያ የማውጣት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

አቶ አሪፍ በከተማው በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች መሬት ሲረከቡ በሊዝ ደንብ ክፍያ ለመፈፀም በገቡት ውል መሠረት ክፍያ እንዲፈፅሙ መደረጉ አግባብ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ "ባለሀብቶቹ አሁን የተጠየቁት ውዝፍ እዳ እንዲከፍሉ ሳይሆን፤ የ2ዐ በመቶ የቅድሚያ ክፍያ ነው" ሲሉ አስተባብለዋል፡፡ የከተማው ባለሀብቶች በሊዝ ህጉ መሠረት የሊዝ ውለታቸውን እንዲፈርሙ፣ አዲሱን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲወስዱ ስራ አስኪያጁ አሳስበዋል፡፡

ሥራ አስኪያጁ የከተማው አስተዳደር ባለሀብቶቹ የሀያ በመቶው የቅድሚያ ክፍያ ውጭ ያለውን የውዝፍ ሂሳብ አከፋፈል በተመለከተ ፍትሀዊ የክፍያ ጊዜ እያመቻቸ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በዚህም የክፍያ ጊዜው እስከ ሀያ አመት ሊደርስ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

በቅድሚያ ክፍያ አከፋፈል መሠረት ሁለት መቶ ካሬ ሜትር የያዘ ባለሀብት ከአርባ እስከ ሀምሳ ሺህ ብር ብቻ የሚከፍል መሆኑን ጠቅሰው፤ "ክፍያው የባለሀብቱን የኢንቨስትመንት ሥራ የሚያደናቅፍ አይደለም" ብለዋል፡፡

ከዚህም ባሻገር በሆቴል፣ በቱሪዝምና በህክምና የተሰማሩ ኢንቨስተሮች ከ50 እስከ 60 በመቶ ቅናሽ እንደሚደረግላቸው አቶ አሪፍ ገልፀዋል፡፡

ስራ አስኪያጁ በከተማው ከተሰማሩት ኢንቨስትሮች አብዛኛው ከ1995 ዓ.ም. ወዲህ ውል የገቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ውዝፍ እዳ በባለሀብቱ ላይ እንደማይኖር ገልፀዋል፡፡ ከባለሀብቶች ጋር ውይይት መጀመራቸውንና ከሀያ በላይ ኢንቨስተሮች ክፍያ መጀመራቸውን አቶ አሪፍ ገልፀዋል፡፡

በሀረር ከተማ እየተካሄዱ ያሉት የልማት እንቅስቃሴዎች አበረታች መሆናቸው ተገለጸ

Posted on April 16, 2008

በሀረር ከተማ ባለፉት ሁለት ዓመታት እየተካሄዱ ያሉት የልማት አንቅስቃሴዎች አበረታች መሆናቸው ተገለጸ፡፡ ይህ የተገለጸው ሚያዚያ 30/2000 ዓ.ም በሀረሪ ህ/ብ/ክ/መንግስት ርዕሰ መስተዳደር የተመራው የክልሉ ካቢኔ አባላት በከተማው እየተካሄዱ ያሉትን የአከባቢ ልማት እንቅስቃሴዎች በጎበኙበት ወቅት ነበር፡፡ በዚሁ መሰረት በከተማው ማዘጋጃ ቤት እየተሰሩ ያሉትን የጁገል ውስጥ ለውስጥ የመንገድ ንጣፍ ስራዎች (Cobble Stone) እንዲሁም በጁገል ውስጥ እየተዘረጋ ያለውን የፍሳሽ ማስወገጃ መስመርና በከተማው የተጀመረውን የ20 ኪ/ሜትር አዲስ አስፋልት ግንባታ ለከተማው ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸውና ስራዎቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ መመሪያ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም የየአከባቢዎቹ ነዋሪዎችም የተጀመሩት የልማት ስራዎች አበረታች መሆናቸውና ለልማቱ መሳካት ከክልሉ መንግስት ጎን እንደሚቆሙ ለካቢኔ አባላቱ አረጋግጠዋል፡፡

View Picture Gallery

Municipal Conference in Harar

Posted on March 03, 2008

Harar municipality conducted a conference on Feb 23,2008 in harar Amir Abdullahi hall.Several hundreds of harar city dwellers have attended the conference,which assessing the past two years performance of the office and evaluated the coming three years action plan of the city,which costs more than 250 million birr.

Harar City Manager, Arif Mohammed ,briefd and presented a detailed report and the up coming plan of action that the  municipality excute with in three years in Harar.The participants up on their part ,have underlined and put thier deep appreciation and concern that the municipality has been achieving the progress twards Harars' development.Finally the conference has vowed to assist and support the the municipalities endevour twards Harars' development.

 

The Defense Army handover land to Harari Region

Jan 29, 2008

It is noticed that harar was a military garrison town during Haileselasse and Derg era .Thus around two million square meters of the city has been occupied by military camps at different directions, that badly hinders the developmental capacity of harar city. After many efforts  been made by the regional government in order to take the land and utilize for different investment opportunities and housing projects since 2000 ,So the federal defense ministry has shown his sincere cooperation to harari regional government to handover some portion of the land occupied  in earlier time to assist the developmental endeavors of the region .

Based on the agreement reached ,on Jan 29,2008 the representative of the federal defense army handover about 270,000 square meters  (27 hectares)  of the land to Harar city manager Arif Mohammed.

 

More than 30 City developmental Projects will be Implemented in Harar by
The coming Four years

 

In order to bring a tremendous change economically and socially in Harar city about 40 different projects that may cost more than 100 million birr will be addressed by the coming 4 years.

The team of experts from Federal Urban Planning Institute on Jan 10th and 11th, 2008, has given a briefing of the project, to the cabinet members and other officials of the region.

H.E President Murad Abdulhad, has forwarded his deep concern that the Integrated Development Planning of the city will highly benefit the economic and social development of Harar and enhance the over all revenue of the city.

Among the Projects:-
Bus terminal development
• City market development
• Heritage development
• waste disposal development
• Micro and small enterprise development
• Municipal finance Improvement
• Land use Planning (master plan development.

and so on...